የኦሮሞ ኢትዮጵያዊነት [የአሰፋ ጫቦን ለከፋ ምክንያት በማድረግ የተጦመረ-በኣፈንዲ ሙተቂ]

August 20, 2015 | በኣፈንዲ ሙተቂ

ብዙዎቻችሁ የኦሮሞ ኢትዮጵያዊነት ትዝ የሚላችሁ “ገንዘቤ ዲባባ ወርቅ አመጣች” ወይንም “ቀነኒሳ በቀለ በኦሎምፒክ ሪከርድ ሰበረ” ሲባል ብቻ ነው፡፡ በሌላ ጊ...ዜ ግን ኦሮሞ ከሌላ ፕላኔት የመጣ ወራሪ፣ ባዳ፣ አሽከር፣ ጂንጂ ጀቡቲ እንደሆነ ነው የሚሰማችሁ፡፡ ኦሮሞ “ኢትዮጵያዊነትን እፈልጋለሁ፤ ኢትዮጵያዊ መሆንን እሻለሁ” ብሎ ሲናገርም እምነት አትጥሉበትም፡፡ ለናንተ ኦሮሞ ኢትዮጵያዊነትን የበጠበጠና ሊበጠብጥ ያሰፈሰፈ እንጂ ከልቡ ኢትዮጵያዊ መሆን የሚችል ህዝብ አይደለም፡፡ የሚገርመው ታዲያ እንዲህ ብላችሁ የፈረጃችሁት ህዝብ “ኢትዮጵያዊ እንዳልሆን ከለከሉኝ፣ ስለዚህ መገንጠል ይሻለኛል” ብሎ በሚናገርበት ጊዜ “እሪሪሪሪ… ሀገር ይያዝልኝ” እያላችሁ መሬቱን የምትደበላልቁ መሆናችሁ ነው፡፡ መራቱ… በዘበዛ ሁላ!!

የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ ጀዋር መሐመድ በአልጀዚራ ቀርቦ “I am Oromo First” አለ፡፡ ይህ ሚሊዮኖች ሲሉት የነበረው ነገር ነው፡፡ ምንም አዲስ ሐሳብ የለበትም፡፡ እናንተ ግን አዲስ ቃል የተናገረ ይመስል “ውግዝ ከመ-አሪዮስ” እያላችሁ ካሷን ወደ ሰማይ አሽቀነጠራችኋት፡፡ እንደ መሳፍንት ዓይነቱን ዝባዝንኬ ዘረኛ ከላይ ላይ እየረገማችሁት በውስጥ ስትባርኩት እንደነበረ ግን ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ድሮም የናንተ ነገር ከዚህ እንደማያልፍ ስለምንረዳ ምንም አልገረመንም፡፡

በኦሮሞ ላይ የሚካሄደው የዘረኝነት ቅስቀሳና የማሸማቀቅ ዘመቻ ቀጥሎ ዛሬ ደግሞ አስገራሚው ሰውዬ ባለተረኛ ሆኖ መጣ! አሰፋ ጫቦ!! እድሜ ልኩን ነፋሱ ወደነፈሰበት አቅጣጫ ሲወዛወዝ የነበረ ፔንዱለም!! ደርግ በተወለደበት የጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር የገዛ ወገኖቹን አስጨፍጭፎት አለፈ፡፡ አሁን ደግሞ ትርፍራፊዎቹ እኛን እንዲበላላቸው በኛ ላይ ለቀቁት! ደግነቱ ኦሮሞ ከኢትዮጵያ አልፎ በምሥራቅ አፍሪቃም በብዛቱ አንደኛ ነው!! ስለዚህ ማንም ሊበላን ቢያሰፈስፍ ብዛታችን ይቀንሳል ብለን አንሰጋም፡፡

እኛም እኮ ከጀዋር ጋር ተናቁረናል፡፡ የኛ ነቆራ ግን I am Oromo First በማለቱ አይደለም፡፡ ብዙ ኦሮሞዎች ለምን እንደዚያ እንደሚሉ በደንብ እናውቃለን፡፡ ባጭሩ የናንተ የዘረኝነት መርዝ ስለሚመዘምዛቸው ነው ከናንተ ጋር መኖርም ሆነ መስራቱን የሚጠሉት፡፡ እኛ ከጀዋር ጋር የተናቆርንበት ምክንያት ግን ከዚህ በጣም ይለያል፡፡ የኛ ጥል መነሻ “መጽሔት ላይ ታተመ የተባለው የዚያ ዘፋኝ ንግግር በመጽሔቱ ላይ አልወጣም፤ ስለዚህ በሌለ ነገር መነሳሳቱ እኛን ይጎዳል፤ አሻጥረኞች ይህንን ተጠቅመው በህዝቦች መካከል ግርግርና ግጭት ሊፈጥሩ ይችላሉ፤ ስለዚህ ብትተው ይሻላል” የሚል ነው፡፡ በዚህ ነበር የተጣላነው፡፡ ይህ አቋሜ አሁንም ትክክል ነው፡፡ ከዚህ ውጪ የተጋጨንበት ጉዳይ የለም፡፡

ኦሆሆይ!!! ኦሮሞ ሲባል ለናንተ በቶሎ ትዝ የሚላችሁ ጄኔራል ታደሰ ብሩ፣ ወይንም አብዲሳ አጋ፣ ወይንም አበበ ቢቂላ፣ ወይንም ደራርቱ ቱሉ፣ ወይንም ሼኽ ሙሐመድ ረሻድ አይደለም፡፡ አዎን ለናንተ ኦሮሞ ማለት ቅዳሜና እሁድ የሰንበት ጠላ እየጠጡ ከጆሊ ባር በረንዳ ላይ “ኦሄ ፈርሶ አያና ወጋ!” ብለው በመጨፈር ፈረንካ የሚለምኑ ዋልጌ ወጣቶች ናቸው፡፡ እነዚያ ስራ ፈት ዋልጌዎች የኦሮሞ ዜግነት መብታቸውን ተነጥቀው የተባረሩ “ከሽለቤዎች” ናቸው እንጂ ኦሮሞ አይደሉም፡፡ መሬታቸውን አርሰው ከቤተሰብ ጋር መኖር ስለማይሆንላቸው ነው የተባረሩት፡፡ በኦሮሞ ደንብ ስራ የማይሰራ ሰው ከማህበረሰቡ ይገለላል፡፡ በነዚያ ወጣቶች ላይም ተመሳሳይ እርምጃ ይወሰዳል፡፡ ሆኖም እንደ ዶሮ እንትን የጠበበው ጭንቅላታቸው ኦሮሞ ሲባል በቶሎ የሚያሳያችሁ እነዚያ ዋልጌዎችን ነው፡፡ እኔ ኦሮሞ ነኝ ስል እንኳ “እንዴ ምን ነካህ! አንተን የመሰለ ሰው እንዴት ኦሮሞ ይሆናል?” የምትሉትን የበከተ ምጸት ማስተናገዱ ራሱ አንድ በሽታ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት በሽተኛ አዕምሮ ይዛችሁ ነው እንግዲህ ለኢትዮጵያ አንድነት እንጋደላለን የምትሉት!! አይ አንድነት!!

ከሁሉም የሚገርመው እንደ ጥብቆ እየሰፋችሁ ለሌላው የምትሸልሙት ሸሚዝ ነው፡፡ ሰውን እየነካካችሁ ምላሽ ሲሰጣችሁ “የበታችነት ስሜት አለብህ” እያላችሁ ጥብቆ ልታለብሱን ትሞክራላችሁ!! ቂቂቂቂቂቂ…!!. ማን ነው የበታች!! ቂቂቂቂ..!! እናንተ የበላይ ናችሁ? እውን አሁን እናንተ የበላይ ናችሁ!! ቂቂቂቂ…
---
እኛ ህዝብ አልነካንም፤ አማራውን፣ ትግራዩን፣ ሀረሪውን፣ አፋሩን፣ ሶማሊውን ሁሉንም እናከብራለን፡፡ “እናንተ” ግን ክብር የማይመጥናችሁ ክብረ-ነክ ናችሁ፡፡ በደንብ አይተናችኋል!! ወስላታ!


አንድነትንም እንፈልጋለን!! ወደፊትም ስለ አንድነት እንናገራለን፡፡ እናንተ የምትሰብኩት ዓይነት አንድነት ግን ጀሃነም ይግባ!! አስራ ሰባት ነጥብ!!

No comments:

Post a Comment